የጤና ባለሙያዎች የህብረተሰቡን ጤና ከመጠበቅ ባሻገር ማህበራዊ ሃላፊነትን ለመወጣት የሚያደርጉት ተግባራት አጠናክረው ማስቀጠል እንዳለባቸው ተገለጸ።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ባለሙያዎች ጋር በጋራ በመሆን በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር የአቅመ ደካማ ቤት ዕድሳት መርሃ ግብር በክፍለ ከተማው ወረዳ 4 አስጀመረ።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሽመልስ ጎዴቦ እንደተናገሩት በክፍለ ከተማው የተለያዩ ተቋማትንና ግለሰቦችን በማስተባበር የክረምት የተለያዩ መርሃ ግብሮችን እያከናወንን እንገኛለን ያሉ ሲሆን በዛሬው ዕለት የጤና ጽ/ቤት ከባለሙያዎች ጋር በመተባበር ያከናወነው ተግባር ሊቀጥል የሚገባና ለሌሎች አርዓያ የሚሆን ተግባር ነው ብለዋል።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሄለን አሰፋ በበኩላቸው የጤና ባለሙያዎች የህብረተሰቡን ጤና ከመጠበቅ ባለፈ ማህበራዊ ኃላፊነት በመወጣት በርካታ ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛል በዛሬው ዕለት ያስጀመርነው የአቅመ ደካማ ቤት ዕድሳት ለዚህ ማሳያ ነው ብለዋል።