የቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የጉለሌ የውበት አክሊል ማሳያ !!

user 07-Jun-2025 ልማት

የቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የጉለሌ የውበት አክሊል ማሳያ !!

‎የቀበና ወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ ፣ የጉለሌ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሽመልስ ጎዴቦ ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች ፕሮጀክቱ እየተተገበረ በሚገኝባቸው ቦታዎች እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ተዘዋውረው ምልከታ በማድረግ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

‎በክፍለ ከተማው ወረዳ 1 እና ወረዳ 2 ፕሮጀክቱን በታቀደለት ጊዜ በጥራትና በውጤት ለማጠናቀቅ የሚያስፈልጉ ለስራው መፋጠን ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራት ላይ ያሉ ተግባራት በአካል የተመለከቱ ሲሆን በፍጥነት እየታረሙ እንዲሄዱ በምልከታው ወቅት አቅጣጫ ተቀምጧል።

‎የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለከተማዋ አዲስ ገፅታን የሚያላብስ፣ የቱሪስት መዳረሻነሻቷን የሚጨምር እና ለነዋሪዎቿ ውብና ማራኪ ገፅታን የሚያጎናፅፍ ፕሮጀክት በመሆኑን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተገልጿል።

Related Post

ልዩ ዜና