አስተዳደሩ በተለያዩ መደበኛና ወቅታዊ አጀንዳዎች ላይ የተወያየ ሲሆን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ሊገነቡ የታቀዱ ፕሮጀክቶች ላይ ዙሪያ ተወያይቷል።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እንደተናገሩት ወቅቱ የበጀት ዓመቱ ጅማሮና ዕቅዶቻችንን ወደ መሬት የምናወርድበት በመሆኑ የህብረተሰባችንን አገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የምንፈታበት ዘርፍ አንዱ ፕሮጀክቶቻችን በመሆናቸው እንዳይጓተቱና በተፈለገው ፍጥነትና ጥራት እንዲጠናቀቅ በትኩረት ሊመራ ይገባል የነዋሪዎቻችን የቤት ችግር ለመፍታትም አቅም በፈቀደ መጠን ለማስተናገድ አስተዳደሩ ጥረት ያደርጋል ብለዋል።